የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ

[ተመዛኞች ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መመሪያዎች በጥሞና ማንበብና ተግባራዊ ማድረግ ይኖርባቸዋል]

**************************************

መመሪያ/Instruction/

  1. በዚህ የኦንላይን ሲስተም መመዝገብ የሚቻለው ከሚያዚያ 07 - 21/2016 ዓ.ም ብቻ ነው።
  2. አመልካቾች በዚህ የኦንላይን ሲስተም ለመመዝገብ ኮምፒውተር መጠቀም ይኖርባቸዋል፡፡ (በሞባይል ስልክ ለመመዝገብ መሞከር ምዝገባውን ያልተሟላ ሊያደርገው ይችላል፡፡)
  3. በዚህ የኦንላይን ሲስተም ለመመዝገብ ተመዛኞች መደበኛ የኢሜይል (email) አድራሻ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ (የ email አድራሻውንና ይለፍ ቃሉን በጥንቃቄ መያዝ ይኖርባቸዋል)
  4. ፈተናውን በድጋሜ (Re-Exam) የምትወስዱ ተመዛኞች ምንም ዓይነት ዶክመንት ማያያዝ (Attach ማድረግ) አይጠበቅባችሁም፡፡
  5. በምዝገባ ሂደት ወቅት ስማችሁ እንዳልተመዘገበ ወይም እንደሌለ የሚገልጽ መልዕክት ከተመለከታችሁ፣ ቀጥሎ በቢጫ ሰንጠረዥ ውስጥ ከሚያመጣላችሁ ዝርዝር ውስጥ ስማችሁን በመፈለግ በስማችሁ ትይዩ የተገለጸውን የትምህርት ተቋም (institution) ከታች ባለው የምዝገባ ሳጥን ላይ Institution / የተማሩበት ተቋም የሚለው ላይ በድጋሚ መርጣችሁ በማስገባት Next/ቀጥል የሚለውን በመጫን ምዝገባውን መቀጠል ይቻላል፡፡
  6. ተመዛኞች የብቃት ምዘና ፈተናውን መውሰድ የምትፈልጉበትን የፈተና ጣቢያ ከተዘረዘሩት አማራጮች ውስጥ መምረጥ ይኖርባችኋል ፡፡
  7. - እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን።
  8. ተመዛኞች ምዝገባቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሲስተሙ የሚሰጣቸውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration ID) መዝግበው /ፕሪንት አድርገው/ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተመዛኞች በምዘና ወቅት እርሳስ፣ መቅረጫ፣ ላጲስ እና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘው መገኘት የሚኖርባቸው ሲሆን ከነዚህ ውጪ የእጅ ሰዓት፣ ሞባይል ስልክ የመሳሰሉትን ጨምሮ ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ ወደ ፈተና ክፍል ይዘው መግባት አይችሉም፡፡
  10. የፈተና ፕሮግራሙን በfacebook: Ministry of health, Ethiopia ማግኘት ይቻላል፡፡
  11. ምዝገባቸውን ጀምረው ሳይጨርሱ ያቋረጡ አመልካቾች ዋናው ገጽ ላይ System login የሚለውን ሊንክ በመጫን email እና password አስገብተው ምዝገባቸውን ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ፦

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

**************************************

መተግበሪያውን መጠቀምዎን በመቀጠል ከላይ የተጠቀሱትን መመሪያዎች እንዳነበቡ ያረጋግጣሉ፣ እንዲሁም ተገቢነት ያላቸውን ውሎች እና ሁኔታዎች ይቀበላሉ ፡፡
I agree and continue / ተስማምቻለሁ ቀጥል